ዛሬም እንደትላንቱ አኩሪው የመተሳሰብ ባህላችን አብሮን አለ
የሀዋሳ ግራንድ ሞል እና የሃዋሳ ሴንትራል ሆቴል ባለቤት ወይዘሮ አማረች ዘለቀ ያለንበትን አስቸጋሪ ጊዜ በመረዳት ህንፃቸውን ለተከራዮ ነጋዴዎች የሁለት ወር ኪራይ ነፃ አርገዋል። ይህም 1,000,000 ብር ይደርሳል።

ከዚህ በተጨማሪ እኝህ ቅን ኢትዮጵያዊ እናት ከኮሮና ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ ስራ ባይኖርም በሆቴላቸው የሚሰሩ ሰራተኞች ወረርሽኙ አንዳች መፍትሔ እስኪገኝለት ድረስ ከጎናቸው እንደማይለዩ ያረጋገጡ ሲሆን የሀዋሳ ከተማም የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል ለሚያደርገው ጥረት የ150.000/የአንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር/ የገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል።
# ግለሰቧ የያንዳንዳችን ሀብት የሁላችን፣ የያንዳንዳችን ችግርም የሁላችን መሆኑን በተግባር አሳይተውናልና ከልብ እናመሰግናለን! #
#የሚሰጡ እጆችን ያብዛልን!#
News and Updates
- የገዳ ሥርዓት በዓለም ቅርስነት የተመዘገበበትን 4ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ለሁለት ቀናት የተካሄደው ዝግጅት ተጠናቀቀ
- የእንጦጦ ፓርክ በይፋ ተመረቀ
- ቱሪዝም ኢትዮጵያ በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ የቱሪዝም መለያ ብራንድ የማስተዋወቅ ስልጠና ሰጠ፡፡
- የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሰርከስ ጥምረት ተመሰረተ
- የጎብኝዎች የደህንነት መጠበቂያ ፕሮቶኮል በተመለከተ ለሼፍ ማህበራት ስልጠና ተሰጠ።
- በሀገራችን የመጀመሪያው የማደጎ ዛፍ ተከላ ፕሮጀክት በላሊበላ ተጀመረ
- በአይነቱ ልዩ የሆነ የእጽዋት ዓለም ፕሮጀክት በቅዱስ ላሊበላ የቱሪስት መዳረሻ ይፋ ሆነ፡፡
- የብርቅዬ ባህላዊ የመድኃኒት ዕጽዋት ችግኞች ተከላ ተካሄደ፡፡
- የባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ዘርፍ አመታዊ የሴክተር ጉባኤ እየተካሄደ ነው፡፡
- ‹‹የኢትዮጵያ ቱሪዝም አጀንዳ!!›› በሚል የተዘጋጀው የቀጣይ አስር ዓመቱ የቱሪዝም ዘርፍ ዕቅድ ለፌደራል ባለድርሻ አካላት ቀርቦ ምክክር ተደርጎበታል፡፡
— 10 Items per Page