መልዕክተ ትንሳኤ!!
ክቡራንና ክቡራት...
የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር ለምትገኙ መላ ኢትዮያውያን የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ-ትንሳኤው በሰላምና በጤና አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡ በዓሉ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ የሚታሰብበት እንደመሆኑ ሁላችንም የልቦና ትንሳኤ እንዲኖረንና ሥርዓተ ዕምነቱ በሚፈቅደውና በሚያዝዘው፤ እንዲሁም የቀደምት አበውን ባህላዊ ትውፊት ተቀብለን ምዕመናን እንደየአቅማችን የታመሙትን ወገኖች በመጠየቅ፣ ለተራቡት በማካፈል፣ ለታረዙት በማልበስ፣ የታሰሩትን በመጠየቅና በመሳሰሉት የበጎ ምግባር መገለጫዎች ተሸልመን በደስታ ማሳለፍ ይኖርብናል፡፡ ይልቁንም ያለንበት ወቅት ዓለማችንም ሆነ አገራችን በCOVID-19 ወረርሽኝ የተነሳ በታላቅ ፈተና ላይ የምንገኝ እንደመሆኑ ችግሩን ለመከላከል እንዲቻል ለሃይማኖት አባቶችም ሆነ ለመንግስት ምክርና ትዕዛዝ ተገዥዎች በመሆን ይህንን ክፉ ጊዜ በጥበብና በብልሃት እንዲሁም በፍቅርና በመረዳዳት ለማለፍ የየበኩላችንን ድርሻ እንድንወጣ አደራ ለማለት እንወዳለን፡፡ ይህንን ማድረግ ከቻልን አፅዋማቱንና ስግደቱን አልፈን የጌታን ትንሳኤ እንደምናከብር ሁሉ ችግሩን በሁላችንም ትጋትና በእግዚአብሔር ቸርነት ተሻግረን የአገራችንን ትንሳኤና ብልፅግና ዕውን እንደምናደርግ ጥርጥር የለንም፡፡
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ከዚህ ፈታኝ ጊዜ አሻገሮ በአንድነትና በፍቅር አገራችንን ለመገንባት ዳግም የምንተጋበትን ጊዜ ያሳዬን፡፡
ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር
News and Updates
- The Geda Panel discussion held on the 4th anniversary of the Geda system recorded in the world heritage
- በአንኮበር ወረዳ በጎረቤላ ከተማ ተገንብቶ ለተመረቀው የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ሙዚየም የተለያዩ ጥንታዊ ቅርሶች ተበረከቱለት
- ለመዲናችን ልዩ ድምቀት!
- ኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ከቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ሰራተኞች ጋር ውይይት አደረጉ፡፡
- የሩሲያ ፌደሬሽን ለኢትዮጵያ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ እርስቱ ይርዳው የዲፕሎማና የሜዳልያ ሽልማት ሰጠች፡፡
- ኢትዮጵያ እና የሩሲያ ፌደሬሽን በባህል፣ በቱሪዝም እና ስፖርት ዘርፍ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውይይት አካሄዱ፡፡
- የኢፌዴሪ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ዶክተር ሂሩት ካሣው ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ጋር ውይይት አደረጉ፡፡
- ስፖርት ለሰላም! በሚል መሪ ሃሳብ የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡
- ዶክተር ሂሩት ካሳው በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ሀማድ አልዶሳሪን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ፡፡
- የአዲስዓለም አድባራት ወገዳማት ደብረጽዮን ማርያም ሙዚየም በአዲስ መልክ ተደራጅቶ ለጎብኚዎች ክፍት ሆነ፡፡
— 10 Items per Page