የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀን በባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ተከበረ
ጥቅምት 2/2013 ዓ.ም
አዲስ አበባ
በሀገራችን ለ13ኛ ጊዜ የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀን ‹‹ሰንደቅ ዓላማችን ለሰላማችን፣ ለአብሮነታችንና ለአገራዊ ብልፅግናችን!›› በሚል መሪ ቃል ጥቅምት 2/2013 ዓ.ም ተከብሯል፡፡
ሰንደቅ ዓላማችን የጋራ ታሪካችን እና የአብሮነታችን ማሳያ በመሆኑ እና ለቀጣይም የሰላማችንና የብልፅግናችን ማረጋገጫ ሁኖ እንዲቀጥል በየዓመቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሚያወጣው የአከባበር መመሪያ መሰረት ከፌደራል እስከ ክልል ባሉ ተቋማት በድምቀት ይከበራል፡፡
የዘንድሮው የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀንም ጥቅምት 2/2013 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡30 ሰንደቅ ዓላማችን በብሔራዊ መዝሙራችን ታጅቦ እንዲሰቀል በታዘዘው መሰረት የባሕልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሰራተኞች ክቡር አቶ ሐብታሙ ሲሳይ የኢፌዲሪ ባሕልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የስፖርት ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል፡፡
‹‹ሰንደቅ ዓላማችን ለሰላማችን፣ ለአብሮነታችንና ለአገራዊ ብልፅግናችን!››
News and Updates
- የገዳ ሥርዓት በዓለም ቅርስነት የተመዘገበበትን 4ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ለሁለት ቀናት የተካሄደው ዝግጅት ተጠናቀቀ
- የእንጦጦ ፓርክ በይፋ ተመረቀ
- ቱሪዝም ኢትዮጵያ በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ የቱሪዝም መለያ ብራንድ የማስተዋወቅ ስልጠና ሰጠ፡፡
- የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሰርከስ ጥምረት ተመሰረተ
- የጎብኝዎች የደህንነት መጠበቂያ ፕሮቶኮል በተመለከተ ለሼፍ ማህበራት ስልጠና ተሰጠ።
- በሀገራችን የመጀመሪያው የማደጎ ዛፍ ተከላ ፕሮጀክት በላሊበላ ተጀመረ
- በአይነቱ ልዩ የሆነ የእጽዋት ዓለም ፕሮጀክት በቅዱስ ላሊበላ የቱሪስት መዳረሻ ይፋ ሆነ፡፡
- የብርቅዬ ባህላዊ የመድኃኒት ዕጽዋት ችግኞች ተከላ ተካሄደ፡፡
- የባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ዘርፍ አመታዊ የሴክተር ጉባኤ እየተካሄደ ነው፡፡
- ‹‹የኢትዮጵያ ቱሪዝም አጀንዳ!!›› በሚል የተዘጋጀው የቀጣይ አስር ዓመቱ የቱሪዝም ዘርፍ ዕቅድ ለፌደራል ባለድርሻ አካላት ቀርቦ ምክክር ተደርጎበታል፡፡
— 10 Items per Page