የባህልና ቱሪዝም ዘርፍን እንዲመሩ የተሾሙ ሚኒስትሮች ከመ/ቤቱ ሠራተኞች ጋር ትውውቅ አደረጉ
ግንቦት 8/2010 ዓ.ም በብሔራዊ ቤተ - መዛግብትና ቤተ - መጻህፍት ኤጀንሲ መሰብሰቢያ አዳራሽ በተካሄደው የትውውቅ መድረክ ላይ ክብርት ወ/ሮ ፎዚያ አሚን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ቡዜና አልከድር፣ የቱሪዝም ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ እና ክብርት ወ/ሮ ብዙነሽ መሠረት የባህል ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አጠቃላይ መካከለኛ አመራሮች እና ፈጻሚዎች ጋር ትውዉቅ አድርገዋል፡፡
ዘርፉን በመምራት ሂደት በሚኖራቸው ቆይታ በሴክተሩ በየደረጃው ያሉ ችግሮችን በመለየት ክፍተቶችን በማስተካከል እና የነበሩትን መልካም ጅምሮች አጠናክሮ በማስቀጠል ላይ እንደሚያተኩሩ ጠቁመው ለዚህም ሁሉም የሚ/ር መ/ቤቱ ሰራተኞች ከጎናቸው እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በቀጣይ በሚ/ር መ/ቤቱ ግልጸኝነት እና ተጠያቂነት የሰፈነበት አሰራር ለማስፈን ልዩ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ አጽንዖት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም የሚ/ር መ/ቤቱ ሠራተኞች የለውጥ መሳሪያዎችን በሚገባ ተረድተው ተግራዊ በማድረግ እና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡና በአዲስ የሥራ መንፈስ ወደ ተግባር በመግባት የተሻለ ውጤት ለማምጣት ከመቼውም ጊዜ በላይ መትጋት እደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል፡፡
News and Updates
- ለመዲናችን ልዩ ድምቀት!
- ኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ከቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ሰራተኞች ጋር ውይይት አደረጉ፡፡
- የሩሲያ ፌደሬሽን ለኢትዮጵያ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ እርስቱ ይርዳው የዲፕሎማና የሜዳልያ ሽልማት ሰጠች፡፡
- ኢትዮጵያ እና የሩሲያ ፌደሬሽን በባህል፣ በቱሪዝም እና ስፖርት ዘርፍ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውይይት አካሄዱ፡፡
- የኢፌዴሪ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ዶክተር ሂሩት ካሣው ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ጋር ውይይት አደረጉ፡፡
- ስፖርት ለሰላም! በሚል መሪ ሃሳብ የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡
- ዶክተር ሂሩት ካሳው በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ሀማድ አልዶሳሪን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ፡፡
- የአዲስዓለም አድባራት ወገዳማት ደብረጽዮን ማርያም ሙዚየም በአዲስ መልክ ተደራጅቶ ለጎብኚዎች ክፍት ሆነ፡፡
- የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ የብራና መጻሕፍት ጉባዔ እየተካሄደ ነው
- የኢትዮጵያ ፊልም ፖሊሲ ወደ ተግባራዊ እቅስቀሴ ተሸጋገረ፡፡
— 10 Items per Page
Chat
Chat is temporarily unavailable.